Saturday, January 14, 2012

መቃብሬ ላይ ቆማችሁ አታልቅሱ!

 

ሜሪ ኤልዛቤት ፍራይ የቤት ዕመቤት እና  የአበባ  ፍቅር ያሰከራት የታወቀች ገጣሚ ነበረች:: ይህችው ሴት እንደ አውሮፓዊያኑ እቆጣጠር ከ1905᎗2004 የኖረች ስትሆን ከዚህ በታች ባቀረብንው “ Do Not Stand At My Grave And Weep ” በተባለ ዝነኛ ግጥሟ ትታወቃለች:: ገና የሶስት ዓመት ልጅ ሳለች ወላጆቿን በሞት የተነጠቀችው ሜሪ በ1927 ዓ/ም ክላውድ ፍሪይ ከተባለ ሰው ጋር ጋብቻ የፈጸመች ሲሆን ይህንኑ ዝነኛ ግጥሟን በ1930ዎቹ መጀመሪያ እካባቢ ለመጻፍ በቅታ ነበር:: ሆኖም እስከ 1990ዎቹ ዓመታት ድረስ የግጥሙ ደራሲ እሷ መሆንዋን እስክትናገር ግጥሙ በማን እንደተጻፈ አይታወቅም ነበር። በኋላ ላይ  ግጥሙ በእሷ ለመጻፉ የተረጋገጠ ሲሆን በ2011 ኖርዌን ለደረሰባት ሃዘን ብሄራዊ ሰሜት መግለጫ ሆኖ አገልግሏል።

image

Do not stand at my grave and weep,

I am not there; I do not sleep.

I am a thousand winds that blow,

I am the diamond glints on snow,

I am the sun on ripened grain,

I am the gentle autumn rain.

When you awaken in the morning’s hush

I am the swift uplifting rush

Of quiet birds in circling flight.

I am the soft starlight at night.

Do not stand at my grave and cry,

I am not there; I did not die.

Saturday, July 30, 2011

Choices

We are what we think.
All that we are arises with our
thoughts.
With our thoughts we make the world.
Speak or act with an impure mind
And trouble will follow you
As the wheel follows the ox that draws
the cart.
We are what we think.
All that we are arises with our
thoughts.
With our thoughts we make the world.
Speak or act with a pure mind
And happiness will follow you
As your shadow, unshakable.
"Look how he abused me and hurt me,
How he threw me down and robbed
me."
Live with such thoughts and you live in
hate.
"Look how he abused me and hurt me,
How he threw me down and robbed
me."
Abandon such thoughts, and live in
love.
In this world
Hate never yet dispelled hate.
Only love dispels hate.
This is the law,
Ancient and inexhaustible.
You too shall pass away.
Knowing this, how can you quarrel?
How easily the wind overturns a frail
tree.
Seek happiness in the senses,
Indulge in food and sleep,
And you too will be uprooted.
The wind cannot overturn a mountain.
Temptation cannot touch the man
Who is awake, strong and humble,
Who masters himself and minds the
dharma.
If a man's thoughts are muddy,
If he is reckless and full of deceit,
How can he wear the yellow robe?
Whoever is master of his own nature,
Bright, clear and true,
He may indeed wear the yellow robe.
Mistaking the false for the true,
And the true for the false,
You overlook the heart
And fill yourself with desire.
See the false as false,
The true as true.
Look into your heart.
Follow your nature.
An unreflecting mind is a poor roof.
Passion, like the rain, floods the house.
But if the roof is strong, there is
shelter.
Whoever follows impure thoughts
Suffers in this world and the next.
In both worlds he suffers
And how greatly
When he sees the wrong he has done.
But whoever follows the dharma
Is joyful here and joyful there.
In both worlds he rejoices
And how greatly
When he sees the good he has done.
For great is the harvest in this world,
And greater still in the next.
However many holy words you read,
However many you speak,
What good will they do you
If you do not act upon them?
Are you a shepherd
Who counts another man's sheep,
Never sharing the way?
Read as few words as you like,
And speak fewer.
But act upon the dharma.
Give up the old ways -
Passion, enmity, folly.
Know the truth and find peace.
Share the way.

The Dhammapada- Translated by Thomas Byrom

Friday, June 24, 2011

ሐሳብ ᎗ ማስታዋል!!

እየመሸ ነው ። የጨፈገገው ምሽት! ፀሃይ ወደማደሪያዋ ካሽቆለቆለች ረፈደ። ደመና በግራጫ ሰማይ ላይ ረብቦ፤ክበቡ ለአይን እየከበደ ሲሄድ ደስ የማይል ስሜት በልብ ላይ ይጭራል። ዝናብ ለረጅም ገዜ ሲዝንብ ቆይቶ ያቆመ ቢሆንም በጨለማው ሽንቁር ውስጥ ሰማዩ እንዳኮረፈ ያስታውቃል። ያለሁበት ክፍል ጨልሞ የሚታየው ከኮምፒተሪ መስኮት የሚወጣውን የፈዘዘ ብርሃን ወድጄዋለሁ። ከኮምፒተሪ ጀርባ ባለው ሰፊ መስኮት ዓለም እንደዝርግ ሳህን ፈሶ ከፊቴ ተሰትሯል። ሁሌም ባተሌ የሆነው የ 395 አውራ ጎዳና ከውሏቸው በሚመለሱ ተሽከርካሪዎች ቀይ የኋላ መብራት መፈናፈኛ አጥቶ ታፍኗል። አይኖቼ የብርሃናቸውን ነጠብጣብ እየተከተለ ይሮጣል። ሃሳቤም እንዲሁ።…………………

ሃሳብ መቼም ቀንድ እንጂ ጭራ የለውም። ይህን ልክ የአንድን መኪና የኋላ መብራት አይን እስከሚችለው ድረስ ተከትሎ ከሌሎች መሰሎቹ ጋር ተደበላልቆ ገጹ ሲጠፋ ያንን በመሸነፍ ስሜት አቁሞ ሌላ ደግሞ በቅርብ ያለን የተሽከርካሪን የኋላ መብራት እንደመከተል አድርገን ልንቆጥረው እንችላለን። ቁም ነገሩ በመጀመሪያውና በኋልኛው መሃከል ያሉ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ የኋላ ተሽከርካሪ መብራቶችን ልብ ሳንላቸው ማለፋቸው ነው። ከነዛ ልብ ሳንላቸው፣ሳናያቸው እና ሳንመለከታቸው ካለፉት የተሽከርካሪ መብራቶች መሃከል አንድ የተለየ መብራት ያለው ተሽከርካሪ አምልጦን ይሆናል። ምን ይሆን!?...........ማን ያውቃል!.........ለሕይወት እንዲሁም ለዓለም ያለንን አመለካከት የሚለውጥ ሃሳብ ሳያጭር ይቀራል!።

እዚህ ላይ ሁለት ሺ ዓመት ወደኋላ ተጉዘን በጥቁር እና ነጭ ቀለማት ጥንታዊቷ አክሱም ውስጥ በኋልኛው ግዜ ቅዱስ የሚሆነውን የሊቁን ቅዱስ ያሬድ ታሪክ መመልከት እንችላለን። እንግዴህ ያኔ ትምህርት አልገባ ብሎት በተደጋጋሚ ፈተና የወደቀው ወጣት ተስፋ በመቁረጥ ከአካባቢው መጥፋት ፈልጓል። ቀኑን ሁሉ በጠራራ ፀሃይ ሲጓዝ ውሎ ስለደከመው በአንድ ትልቅ የዛፍ ጥላ ስር አርፏል። የአካባቢው ፀጥታ፣ በዛፎቹ ዙሪያ ያለው ነፋሻማ አየር ለፍጹም የግል ተመስጦ የሰጠ ነው እንበል። መቼም ነፍሱ ለትልቅ ነገር የተፈጠረ ነው እና በአረማሞ ከፊት ለፊቱ ባለው ዛፍ ላይ የሚርመሰመሱት የጉንዳን መንጋዎች ላይ አይኑን ተክሎ ከፈጣሪው እና ከራሱ ጋር በጥሞና ሙግት ገጥሟል። በብዙ ሺ የሚቆጠሩት የጉንዳን ሰራዊት ከመሪት ወደዛፉ ቅጠል እና ቅርንጫፍ በሰልፍ የሚያደርጉትን ጉዞ ፤የተበጣጠሰ ሃሳቡን እላያቸው ላይ አሳፍሮ፤ የሚሄደውን በመሸኘት እንደገና አዲስ ከሚመጣው ጋር ሽቅብ ወደላይ ይነጉዳል። በዚህ ፍጹማዊ እርጋታን በተላበሰ ተመስጦ የሚሞግተው ሃሳብ ግልጽ ያለና የጠራ በመሆኑ ነፍሱ ሰማያተ-ሰማያት በመውጣት የዕውቀትን ሚስጥር እና ከዛም የሚገኘውን ማስተዋል ለመጠየቅ አስችሎታል። ከሁሉም አስገራሚው ነገር ከፈጣሪ ምላሽ ያገኘበት ሁኔታ እና ያንን ለመተርጎም የተቸረው ተሰጥኦ ነበር።

ወጣቱ ቅዱስ ያሬድ ከእነዛ የዛፉን ግንድ ሽቅብ ወደላይ ከሚወጡት ጉንዳኖች መሃከል በተደጋጋሚ ለመውጣት እየሞከረ ከመሃል ሳይደርስ የሚከሰከስ ጉንዳን አይኖቹን ስቦታል። እየጀመረ ሳይጨረስ ከመሃል እየተንደረደረ ቁልቁል የሚወድቀው ጉንዳን ሳያሰልስ ለመውጣት የሚያደርገውን ሙከራ ገርሞት በንቃት መቁጠር ይዟል። አንድ………॥ሁለት……॥ሦሥት…………।ሰባተኛውን መቁጠር እንደያዘ፤ ጉንዳኑ ሙከራው ተሳክቶላት ጉዞውን ከሌሎች ጉንዳኖች ጋር በመቀላቀል በአሸናፊነት ቀጠለ። ይህኔ የዕውነትም የዕውቀትም መገለጥ ወደሱ ይመጣል። “ ይህ ቅንጣት ፍጡር ተፍጨርጭሮ አሰበበት ለመድረስ የቻለ እኔ በእግዜር ዓምሳል የተፈጠርኩ የፈጣሪ ታላቅ ስራ፡ እንዴት ትምህርቴን መጨረስ ያቅተኛል!? ”

ከዚህ በኋላ ያለው ታሪኩ እንደሚታወቀው ትምህርቱን ትቶ ለመጥፋት ያሰበውን በመቀየር ወደ ትምህርት ቤቱ በመመለስ ያቋረጠውን ትምህርት ጨርሶ ከነ ሞዛርት እና ቤትሆቨን የሚበልጥ የዜማ ሊቅ ይወጣዋል:: ተመስጦ ከማስተዋል ጋር ሲዋሃድ ይሏል እንዴህ ነው!!

ተመስጦ ወደ ውስጣችን አለያም ወደ ነፍሳችን ጥልቀት በመመልከት ይጀምራል። በእርግጥ እንደሚባለው ወደ ውስጣችን መመልከት ያስፈራል። የነፍሳችን በር ጨለማ የዋጠው፡ በነውጥ የተሞላ ውካታ ነው። ያንን አልፈው እጥልቅት ያሚገኘውን ሰላም መመልከት የሚችሉ ድፍረቱ የታደላቸው በጣም ጥቄቶች ብቻ ናቸው።

ሰው ወደ ነፍሱ ጥልቀት ዘልቆ ማየት ከቻለ ውጫዊውን ቁሳዊ ዓለም መገንዘቡ እርግጥ ነው። ወደ ውስጥ ለመመልከት ሳይደፍሩ ውጫዊውን ዓለም መረዳቱ የማይታሰብ ነው። የነፍስህን ሙግት ለማቅረብ ወደ ውስጥህ ጥልቀት በተመስጦ ታያለህ። ምላሹ ግን ያለው ቁሳዊው ዓለም ላይ ነው። የነፍስህ ጥልቀት ከውጫዊው ዓለም የምታገኘውን ምላሽ ለመረዳት የሚያስችልህን ማስታዋል ይለግስሃል።

ወደ ውስጥህ በተመስጦ በተመለከትክ ቁጥር ምንጩ ወዴት እንደሆነ ወደ ማታውቀው ብርሃን እየቀረብክ ነው። በህይወትህ ለመጀመሪያ ግዜ እራስህን መገንዘብ ትጀምራለህ። አንተ ማንም አይደለህም፡ እራሱን የምታየው ብርሃን እንጄ! ደግሞም የዕሳቤህና የግንዛቤህ የንጋት ብርሃን ነጸብራቅ ነህ!!!

ሆኖም ሁሉም ነገር ግን ያልፋል። ዕሳቤህም᎐᎐᎐᎐᎐᎐᎐የተገነዘብከውም ቁሳዊ ዓለም!! የሚቀረው ብርሃኑ ብቻ ነው። በሊቁ ቅዱስ ያሬድም የሆነው ይሄው ነበር።

የከርሞ ሰው ይበለን!!

Sunday, June 12, 2011

ግጥም ድሮ ቀረ___እንዳቀረቀረ! 2

እንኵን አልታደምክ ከምንተሼ ደንቆሮ መኅል ጫጫታ

ለዓለም ቢገባም ባይገባም ይሻልሃል ጸጥታ!

ያስቀናል ተከበህ በብህትውና የብቸኝነት ጥላ

ከሃሳብህ ዘባተሎ እየተረተርክ ስትጥፍ መሸሸጊያ ከለላ::

እሩቅ_እሩቅ ቀስረህ በአይኖችህ ጥልቀት

ከአድማስ ጥግ መጥቀህ ከሰመያተ_ሰማያት::

በዝምታህ የምትሞግተው ኣምላክ እንዳለ

ይናገራል መንፈስህ ኣካልህን ጥሎ የኮበለለ::

ይታያል በብቸኝነትህ ውስጥ ሰላም _ በሰላምህ ጻጥታ

ምሥጢር የሚነግሩህ መለዓክት በሰመያተ ሰማያት ሹክሹክታ::

ደግሞም አለ ሙዜቃ _ የሚሰማ የተፈጥሮ እንጉርጉሮ

በነፍስህ ጥልቀት የሚንሸዋሸው ጽናጽል _ የሚመታ ከበሮ::

ውበት ነው ቅኝቱ

ዕውነት ነው መልዕክቱ::

ዜማው ለዓለም ባይገባም

ለአንተ እንጄ ኣይጠቅምም

___________ ለማንም!!

Friday, February 25, 2011

ቆንጆዎቹ እየመጡ ነው!

ሙላቱ ነኝ! ባሌ ከሰማይ ጥግ ስር በዓለም ከተረሱ ቦታዎች በአንዱ የተወልድኩ። ብዙም የመፃፍ ልምድ የለኝም። የብሎጉን ባለቤት በእጅ በእግር ለምኜ የሚሰማኝን እንድፅፍ ስለፈቀደልኝ ትንሽ የልቤን መተንፈስ እፈልጋለሁ። ለዛውም ከ ‘ፖለቲካ በቀር ! ’ የሚል ገደብ ተጥሎብኛል። ፖለቲካ ያልነካካው ምን ‘ ዓይነተኛ ’ ነገር ማሰብ እንደሚቻል ዓላውቅም። ይኄ መገናኛ ብዙሃን የሚባል ነገር ተፈጥሮና በየግዜው እድገቱ በመፋጠን ተሻሽሎ ፥ አዳዲስ የኤሌትሮኔክ መገናኛ እና መላጫ ዘዴዎችን አካቶ እዚህ ቢደርስም የዓለም “ ትላልቁ ሰው ” ሁላ ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ስላዋለው ተራው ሕዝበ-ግባስ ከጥላቻ የተነሳ እስከ ዝንተ ዓለም እንዳይርቀው እሰጋለሁ።

ባዚያን ሰሞን ምን እንዳንቀዠቀዠኝ አላቅም……….ያገሪ ቴሌቪዥን ባህር አቋርጦ እዚህ ያለሁበት አገረ - ቨርጄኔያ ድረስ መተላለፉ አስደስቶኝ፤ አብራኝ የምትሰራውን ነጭ እንድትመለከት በመጋበዝ የሚተላለፍበትን መስመር ቁጥር ነገርኳት። በነጋታው ሰላም እንኳን ሳትለኝ አስቀድማ፥

“ ሙላቱ…..ቴሌቬዥንህን አይሁለህ። ምንም ለዓይን ደስ የሚል ነገር የለውም። ከፈራረስ ጎጆ እና ልብሱ እላዩ ላይ ካለቀ ችግረኛ በቀር የሚታይ የላችሁም እንዴ! ” አለች ፊቷን አጥቁራ።

መሪት ተከፍቶ ቢውጠኝ እንዲት ደስ ባለኝ! በሃፍረት ፊቴ ወዝቶ እና እየተርበተበትኩ..

“ እረ!......ብዙ ውብ ነገሮች አሉን።………ያለው መንግስት ከውጬው ዓለም ገንዘብ ለማግኛት ብሎ ነው ችግረኞችን የሚያሳየው ። ” አልኩ።

ለእሷ ብዙዎቹ የአፍሪካ መንግስታት እንዲሁ ናቸው ። ያልኩትን አምና በመቀበል ጭንቅላቷን እየነቀነቀች ሄደች። በውስጤ እዛ የማይረባ የቴሌቬዥን ጣቢያ ላይ የእርግማን ማእቱን አወረድኩበት። እስቴ አሁን እሷ በከፈተችበት ሰዓት እኔ ስሯሯጥ ያደኩባቸውን የባሌ ተራራዎች፣ በውስጡ የያዛቸውን ብርቅዬ እንስሳት እና እፅዋት እንዲሁም ፍሪያቸው የተንዘረፈፈውን ሰፋፊ የገብስ ማሳዎች ቢያሳዩ። እየተንፎለፎለ ከሚወርደው የአባይ ፏፏቴ ስር ንጹህ የአገር ልብሳቸውን የለበሱ የአገር ባህል እስክስታ የሚወርዱ ቆንጅዬ ልጃገረዶችን ቢያሳዩ……………….የሶፍ ኦመር ዋሻ፣ የሓረር ግንብ፣ የጎንደር አብያተ መንግስታት፣ የአክሱም ሃውልት………………..ብዙ ብዙ ማለት ይቻላል።

ለነገሩ ድሆች ነን። ዘፋኙ ልትወድቅ አንድ ሃሙስ ከቀራት ደሳሳ ጎጆ ስር ላለችው እናቱ ወይ ፍቅረኛው ይዘፍናል። የቴያትሩ መቼት በገማና በበሰበሰው የህብረተሰብ አዘቅት ስር ይከውናል። የንን ደሳሳ ጎጆ አፍርሶ ሕንጻ ስለመገንባት የሚያቀነቅን የለም። ህብረተሰቡን አንቀሳቀሶ በሕብረት በመስራት እንዴት ከድህነት መላቀቅ እንደሚቻል የሚያሳይ የተውኔት ጸሃፊ ገና አልተፈጠረም። እንደተባለው ድህነታችን የገንዘብ እና የአስተሳሰብ ብቻ አይደለም። ያቼ አገር ያለ ዕውቀት እና ያለችሎታቸው ፡ አለቦታቸው የሚገቡ ሰዎች መበራከታቸውም ጭምር ነው። ካድሪው ጋዜጠኛ ነው፤ ፍፁም ዓለማዊው ሰው የኃይማኖት አባት ይሆናል፤ መምህሩ አቃጣሪ ነው፤የፊዚክስ ሊቁ የፓርቲ አይዲዮሎጄ ፍጹማዊ አመንጬነቱን የሚነጥቀው የለም፤ ወንጀለኛው በዳኛንቱ ታምኖበታል፤ ቤተሰብ በማስተዳደር ያልተፈተነው የአገሪቱ እጣ ፋንታ እጁ ላይ ወድቆ ያለ አዛዥ - ናዛዥ ብቻውን ይወስናል።ሁሉም ነገር ወይ ከሚገባው በላይ ነው። ወይ ከሚገባው በታች ነው።

ዛሪ…………. ዛሪ አንድ ነገር እየገባኝ ነው። የአንድን አገረ ዕድገት ደረጃ፥ የቴሌቪዥን ጣቢያዋን በማየት መገመት ይቻላል። ኤቴቬ አገሪቷ ያስመዘገበችውን ዕድገት በፈለገው ቁጥር አስልቶ እያቀርብ ለማሳመን ቢደክምም እንዲህ እንደ ሚስስ ሲንዲ ያሉ ሰዎች ቴሌቪዥን ጣቢያው የሚናገረውን ቋንቋ መስማት ባይችሉም እንኳን ምስሉን ብቻ በማየት የአገሪቱን የድህነት አረንቋ መገንዘብ ችለዋል። ለእነሱ ኤቤሲ እና ፎክስ ላይ ያለው ምቾት እና ድምቀት ኤቴቪ ላይ የለም።

ኤቴቪ አገሪቱ ያለችበት ደረጃ እና ሁኔታ ማሳያ ነፀብራቅ ነው። የሕዝቡን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ዕድገቱን በጥቅሉ በዚህ የመገናኛ ብዙሃን አንድ ዘርፍ ማየት ብቻ ሳይሆን በተናጥልም የአዘጋጆቹን የሥነ - ምግባር ደረጃ እና ሙያዊ ብቃት በመመልከት በሌሎች በርካታ መንግስታዊ መሥሪያ ቤቶች እነማን እንዳሉ አመልካች ነው።

ሰሞኑን የዓረቡ ዓለም በለውጥ ማዕበል እየተናጠ ነው። ኤቴቪ መላውን የሰው ልጅ ትኩረት ስለሳበው አብዮቱ አንዳች ያለው ነገር ባይኖርም በጭቆና ቀንበር ውስጥ ያሉት ህዝቦች ያነሱት የለውጥ ዓመፅ ጎረቤት አገር ደርሷል። ያሉብን ችግሮች መበራከት እና በህዝቡ መሃል መብሰልሰል ቀጣዩ ወረ - ተራ እኛ መሆናችንን አመልካችነቱ “ ማነው…..ባለሳምንት!? ” አስብሎ እጣ የሚያስወጣ አይደለም። ቁም ነገሩ ከሥርዓት እና ከግለሰቦች ለውጥ ባሻገር የባህል አብዮት ያስፈልገናል። በማሽን ውስጥ ተጠፍጥፎ እንደሚወጣ ሳሙናና ከረሚላ “ ኢትዮጵያዊ ሰው ” የሚፈጥር አብዮት ያስፈልገናል።

አገሩን የሚወድ፣ ታክስ የማያጭበረብር፣ የፈረንጅ አገር የማይናፍቅ፣ ለእውቀት እና ለእድገት የሚተጋ…………እራሱን እና ወገኖቹን ለመለወጥ የሚሰለፍ፣ የአከል ብቃቱ የዳበረና ሱሰኛ ያልሆነ፣ የሞራል ስብዕና የተላበሰ፣ በሙስና ያልተዘፈቀ፣ ሰውን እና የሰውን ልጅ የሚያከብር እና የሚፈቅር ህብረተሰብ የሚፈጥር አብዮት ያስፈልገናል። ይህን አብዮት ለማካሂድ የግድ “ ማኦ ” ኢትዮጲያዊ ሆኖ እንዲፈጠር መጠበቅ የለብንም።

ህዝባዊው ዓመጽ ትክክለኛ ሰዎችን ወደስልጣን የሚያመጣ ከሆነ ይሄ በተጨማሪ መምጣት አለበት የምንለው የባህል አብዮት የመደረጉ ዕድል ከፍተኛ ነው የሚሆነው።ያለያማ “ ኢቴቪ ” እና “ ሃገሪቱ ” የአዘጋጅ ለውጥ ብቻ አርገው በዛው ዕትም የሚቀጥሉ ከሆነ የምንናፍቃቸው “ ቆንጆዎቹ ” እስኪፈጠሩ ዓመታት መጠበቃችን ነው። የሆኖ ሆኖ እንደማንም ለሃገሩ ቅን እንደሚያስብ ዜጋ የምንመኛቸው አብዮቶች ሁሉ ተሳክተው የተሻለ ነገር እንዲመጣ ተስፋ በማድረግ ልሰናበት። በእርግጥ ቆንጆዎቹ እየመጡ ነው!!!!!!!

Thursday, February 24, 2011

Advice To A Son

 

 

by Ernest Hemingway 1988-1961

written in 1931

Never trust a white man,
Never kill a Jew,
Never sign a contract,
Never rent a pew.
Don't enlist in armies;
Nor marry many wives;
Never write for magazines;
Never scratch your hives.
Always put paper on the seat,
Don't believe in wars,
Keep yourself both clean and neat,
Never marry whores.
Never pay a blackmailer,
Never go to law,
Never trust a publisher,
Or you'll sleep on straw.
All your friends will leave you
All your friends will die
So lead a clean and wholesome life
And join them in the sky.

Friday, December 10, 2010

የቴክኖሎጂ ሥሥት!

ጥሎብኝ ለኤሌክትሮኒክስ ነገሮች ስሜቴ ስሡ ነው። የምፈልገውን አግኝቼ ሁለ - ነገረ ሥራውን ካወኩት በኋላ እስለቻለሁ። ደግሞ ሌላ …….ሌላ አዲስ ነገር ለመፈልግ እነሳሳለሁ። ዘመኑ የቴክኖሎጂ ዘመን ነው። ፈጠራዎች ሁሉ ገበያ ተኮር ናቸው። የሰውን ስሜት…………ቀልብ እንዲሰቡ አድርገው ፈጣሪዎቻቸው ይፈጥሯቸዋል። ኮምፒተር፣ አይፓድ፣ አይፎን፣ ሳንዲስክ፣ኢሪደር……………የሸማቾቻቸውን አትኩረት የሳቡ የዘመኑ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎች ናቸው። እንዲያም በመሆኑ ፊት- ፊት ይገኙባቸው ከነበረው እንደ ቤስት ባይ ካሉ የኤሌክትሮኔክስ መሸጫ ሱቆች ውጭ በየልብስ መሸጫው መደብር፣በየሴቬኤሱ እና መሰል ሱቆች ማየት የተለመደ ነው።

የዴል ኮምፔተሪን እወዳታለሁ። ይህች የቪስታ ቨርሽን ያለባት ኮምፒተሪ አሁን ያለችበት የተሟላ ደረጃ ለመድረስ የኔን ያላስለሰ ጥረት ጠይቃለች። ቀድሞውኑ የነበረኝ የኮምፒተር እውቀት እዚህ ግባ የማይባል የነበረ ቢሆንም እራሴን በራሴ በማስተማር ለኮምፒተሪ የዋልኩላትን ውለታ ያህል እሷም በምላሹ ታላቅ ውለታ ውላልኝለች። ከሁሉም- ከሁሉም ውስጠ ገበናዋን ካወኩ በኋላ ለሥነ-ጹሁፍ ያለኝን ፍቅር በመረዳት አንድ ደረጃ ወደ Blog ( መቅደጃ ) አሸጋግራኛለች። ዕድሜ ለmicrosoft word ይህን የምጽፈውን ጹሁፍ ጽፊ ከጨረስኩ በኋላ sign በማድረግ ብሎጌ ላይ እለጥፈዋለሁ። ይህ የማይክሮ ሶፍት ወርድ ፕሮግራም ብሎጌ ላይ ለመለጠፍ እክል ቢያጋጥመው windows live writer የሚባለው ፕሮግራም ላይ copy-paste በማድረግ አልያም እዛው windows live writer ላይ የምፈልገውን በመጻፍ እንደተለመደው sign በማድረግ ብሎጌ ላይ መለጠፍ እችላለሁ። ሌላም ሌላም ስለኮምፒተሪ ማውራት እችላለሁ። በላይዋ ስለጫንኩባቸው ሶፍት ዌሮች፤ ስለምን ስለምን እንደሚጠቅሙኝ ለማውራት ዛሪ የተነሳሳሁበት ዓላማ ስላልሆነ ልለፈው።

Windows7 ከመጣ በኋላ ኮምፒተሪ አስጠላችኝ። አዲስ ነገር የማወቅ ፍላጎቴ አለመጠን ተነሳሳ። ይህች የኔዋ ዴል ቪስታ ያረጀች መሰለኝ። ይህንኑ አዲስ እትም የማግኘት ሱስ አንቀዠቀዠኝ። ስለሁኔታው ለባለቤቴ አዋየኋት።

“ ዓመት ሳይሞላህ ሌላ ኮምፒተር…………ግፍ ነው! ” አለች። አልተከራከርኳትም። ማምሻውን ከስራ ስትመለስ ደግሞ ጥሩ ትምህርት ሰጠችኝ።

“ ባለቤቴ windows 7 አሰኘኝ ይለኛል ብዬ ለ ሚስተር ትረል ነገርኩት። ምን እንዳለኝ ታቃለህ! ”አለች እየሳቀች።

“ እሺ ምን አለሽ!? ” አልኩ። የስራ ባልደረባዋ እኔን የሚደግፍ ነገር ይናገራል ብዬ ለመስማት በመጓጓት።

“ አማረው!? ቤሊጌት እራሱ የለውም ብለሽ ንገሪው!! አለኝ እየሳቀ። ” አለች።

በሃፍረት ኩም ብዬ ጸጥ አልኩ። በዛን ሰሞን እራሱ ቤሌጌትን በሃብት የበለጠው ሜክሲኳዊ ቢሊየነር ኮምፒተር ነካክቶ እንደማያቅ ከሰማሁ በኋላ ይህንኑ አዲስ ኮምፒተር የማግኘት ፍላጎቴ እውስጤ ሞተ።

ሰሞኑን ዓመል ነው እና ኢሪደር ( ereader ) የማግኘት ምኞት ተቀስቅሶብኛል። አልፎ አልፎ የምጎበኛቸው ድህረ-ገጾች ለፍላጎቴ መባባስ አስተዋጾ አድርገዋል። እነዚሁ “ መረጃ ገደብ ሊደረግበት አይገባም ” የሚሉ ድህረ-ገጾች በነጻ ኢሪደር ላይ መፀሃፍትን ዳውን ሎድ በማድረግ የመፀሃፍት አፍቃሪዎች በዘመኑ ቴክኖሎጂ እንዲጠቀሙ ያበረታታሉ። ስሜቴ ይህንኑ ነገር አግኝቶ ለመዳሰስ ተንቀዠቀዠ። ለመጸሃፍት ካለኝ ፍቅር እና ለኤሌክትሮኔክስ ካለኝ ሱስ መጽሃፍትን እንዲህ በዘመኑ የተራቀቀ ቴክኖሎጂ በቀላሉ አግኝቶ ለማንበብ ተስገበገብኩ። ደግሞም እንደኔ ዓመል ላለበት አጓጔ ነገር ነበር።

ባለፈው የፈረንጆች ብላክ ፍራይዴይ እለት ወደ ቤስት ባይ በመሄድ literati ኢሪደር ( ereader ) ገዛሁ። ቀሼም ገበያተኛ! በግዜው ይሀው ኢሪደር እንዲኖረኝ ከመጓጓቴ የተነሳ የትኛው የተሻለ መሆኑን ለመመራመር ለእራሴ ዕድል አልሰጠሁትም። እቤቴ መጥቼ ስመለከተው መሳሳቴ ገባኝ። ቀርፋፋ፣ ባትሪው ዕድሜ የሌለው፣ እንዲሁም የwi-fi ኮኔክሽኑ በጣም ደካማ የሆነና ተስፋ አስቆራጭ ሆነብኝ።ይበልጥ ደግሞ ያበገነኝ በፒዲፍ የተጻፉ መጻህፍቶችን እላዩ ላይ ጭኜ ማንበብ አለመቻሌን ስረዳ ነበር። የዚሁ ኢሪደር በጎ ጎን ተደርጎ የሚወሰደው ከkobe 150 ክላሲክ መጸሃፍትን በነጻ መጫን መቻሉ ሲሆን፤ እሱም ቢሆን ክላሲክ መጸሃፍትን ለማንበብ ከሚያስፈልገው ግዜ እራጋታ ጸጥታ እና ሰላም አንጻር ፤እዚህ ውክቢያና ጥድፊያ ለሞላበት የአሜሪካ ኑሮ የሚመረጥ አይደለም። ከሁሉም----ከሁሉም ስለዚሁ ኢሪደር ጉግል ላይ ከተጠቃሚዎች የተሰጠውን አስተያየት ሳነብ ፍጹም መሳሳቴ ገባኝ። አንድ የዚሁ ኢሪደር ተጠቃሚ በሰጠው አስተያየት “ ይህ ኢሪደር የሚባል ነገር በ1990ዎቹ የተፈጠረ ቢሆን ኖሮ literati የዛን ዘመን ቴክኖሎጂ ተደርጎ ሊቆጠር ይችላል። ”

የዛን ቀን ለሌት እንቅልፍ ሊወስደኝ አልቻለም። በራሴ ስናደድ እና ስበሽቅ አነጋሁ። በነጋታው ኢሪደሩን ወደገዛሁበት መደብር በመሄድ ገንዘብ በመጨመር በNook colour ቀየሩልኝ። ይህኛው ኢሪደር ( ereader ) ፈጣን፣ ባለቀለም፣ ፒዲፍ መፅሃፍትን ማንበብ የሚያስችል MP3 ሙዚቃ እላዩ ላይ ጭኖ እያነበቡ የሚያዳምጡበት፣ እንዲሁም wi-fi ኮኒክሽኑ ፍጹም ቅጽበታዊ በመሆኑ በቀላሉ ከኢንተርኔት ጋር የሚያገናኝ ስለሆነ አስደሳች ነበር።

ዛሪ ከኢሪደሪ ( ereader ) ጋር ፍቅር ወድቄያለሁ። እላዩ ላይ እንዲኖረኝ የምፈልጋቸውን የታዋቂ ደራሲያንን የታሪክ፣ የፍልስፍና እንዲሁም የሃይማኖት እና የሳይኮሎጂ መጸሃፍት ጭኜባቸዋለሁ። የምወዳቸውን እና የማፈቅራቸውን የፀጋዬ ገብረ መድህንና የገብረ ክርስቶስ ደስታ በፒዲፍ የተዘጋጁ የአማርኛ ግጥም መጸሃፍቶቻቸውን በመጫኔ በፈለግሁበት ቦታ እና ሰዓት ለማንበብ እችላለሁ። ለቴክኖሎጂ ምስጋና ይግባ እና የእኔ ኢሪደር ( ereader ) ለጊዜው የመጨረሻው ሌተስት ሳይሆን አይቀርም። ምናልባት በነጋታው ከኔ ባኋላ የተሻሻለው ወጥቶ ይሆናል…………እኔ ግን ሌላ ቴክኖሎጂ መጥቶ ቀልቤን እስኪሰልበው ድረስ በዚሁ ኢሪደሪ ( ereader ) መደሰቴን እቀጥላለሁ።

Tuesday, November 23, 2010

እውን እስታሊን በመርዝ ነው የሞተው!?

በመጋቢት ወር 1953 የቀድሞዋ ሶቬዬት አንባገነን መሪ ጆሴፍ ስታሊን ጭንቅላቱ ውስጥ ደም በመፍሰሱ ምክንያት ለህልፈተ ህይወት ሲዳረግ የሩሲያ ጋዜጦች ለታላቁ መሪያቸው የሚቆጥቡት እንባ አልነበራቸውም። ልባቸው በሃዘን የተነካ ንግግር አድራጊዎች ስታሊንን ‘ ጄኔየስ እና የሩሲያን ህዝቦች የታደገ አምላክ’ ሲሉ ገለጹት። በኋላም አስከሪኑ በቀዩ አደባባይ ከሌኒን አጠገብ በክብር ሲያርፍ ሺዎች በዕንባ ሊሰናበቱት ሰልፍ ያዙ።

በ1956 ዓ/ም ኔኪታ ክሩቼቭ መጋረጃውን ገፎ “ ስታሊን ለ43 ሚሊዮን ሰዎች መገደል፣ መጥፋት እንዲሁም በባርነት መጋዝ ምክንያት የሆነ ጭራቅ ” መሆኑን እስኪገልጽ ድረስ ማንም ምንም ለማለት አልደፈረም። በርግጥ ክሩቼቭ በፓርቲው ስብሰባ ላይ ደፍሮ እስታሊንን የሚወነጅል ንግግር ሲያደርግ የደበቀው እና ጨምሮ ያልተናገረው ሌላ ታሪክ እንዳለ ግልጽ ነበር። ‘ ዛሪ……ዛሪ የሚወጡ ማስረጃዎች እንደሚያሳዩት ’ ይለናል የ World’s Great Mysteries ደራሲ John Pinkney ‘ ታላቁ አንባገነን ህይወታቸውን ለማዳን እና ከምዕራቡ ዓለም ጋር የሚጀመረውን የኒኩሊየር ጦርነት ለማስቀረት ሲሉ አራት ፍርሃት የዋጣቸው ጓደኛሞች በአይጥ መርዝ መርዘው ሳይገድሉት አልቀሩም። ’

ታሪኩ እንደዚህ ነው……………………………………………………

የህይወት ዘመን የሶቬት ህብረት መሪ በተዝናና ስሜት ላይ ነው ያለው። በክሪሚሊን ቤት መንግስት ባለው የግል ሲኒማ ማሳያ የኮሜዲ ፊልም እያየ በታላቅ ደስታ ውስጥ የነበረ ሲሆን አሁን ደግም ምቾት ባለው ክፍል ውስጥ ከፓርቲው የማዕከላዊ አባላት 4 ሰዎች ጋር እየተዝናና ነው። እንሱም ላቨረንቲይ በሪያ፣ ጂኦርጂ ማለንኮቭ፣ ኒኪታ ክሩቼቭ እንዲሁም ኒኮላይ ቡልጋኒን ናቸው።

እንደ ሁሌው ስታሊን ጨዋታውን ተቆጣጥሮታል። ዙሪያውን የከበቡት የፖለቲካ ጓዶቹ ብዙውን ግዜ በንግግሩ ፈገግ በማለት ወይ በአድናቆት ጭንቅላታቸውን በመነቅነቅ አልያም የሚጠጡትን መጠጥ ከመጎንጨት ባለፈ ድምጻቸው አይሰማም። በጠረጲዛው ላይ ብራንዲ፣ ቮድካ እንዲሁም ሊላ የአልኮል መጠጥ አይታይም። መሪው በማዘዙ ምክንያት ዛሪ የማጃሪ ወይን ተራ ሲሆን ከጥሩ ጨዋታ ጋር የተሻለ እንደሚሆን አያጠራጥርም።

ክብ ስርተው ከተቀመጡበት ወንበር ጀርባ ባሉ ሁለት ረጃጅም ጠረጴዛዎች አጠገብ አንዳች ነገር ቢፈጠር ቅጽበታዊ እርምጃ ለመውሰድ በተጠንቀቅ የቆሙ የክብር ዘቦች አሉ። ከእንሱ አንዱ አሌክሲ ራይቢን በኋለኛው ግዜ ስለዛች ቀን ምሽት An Iron Soldier የተባለ ማስታዋሻ የጻፈ ሲሆን ስለተከሰተው ነገር ብዙ የተብራራ ነገሮችን ይዟል።

በዚያች ምሽት አለ- አንዳች የውስጥ እውቀት ከውጭ ቆሞ ለሚያይ ታዛቢ የስታሊንን ወዳጆች ደስተኛነት እና ፍጹም በደህንነት ውስጥ መኖራቸውን ቢገምት አይፈረድበትም። እውነታው ግን ሁሉም በፍራቻ ባህር ውስጥ ስምጠው ነበር። እያንዳንዳቸው ይህ ጨካኝ እና ምህረት የለሽ ሰው በማንኛውም ግዜ ተነስቶ ሊገላቸው አለያም ከከባድ ስራ ጋር ማጎሪያ ቦታዎች ሊያግዛቸው የሚችል አደገኛ ፍጡር መሆኑን አላጡትም። አራቱ ጓደኛሞች እስታሊን በፓርቴው ማዕከላዊ አባላት ላይ የማጽዳት ዘመቻ ሊያካሂድ እንዳሰበ መረጃው ደርሷቸዋል። ስለጉዳዩ በመጀመሪያ አንስቶ ከጓደኞቹ ጋር ለመወያየት የደፈረው ክሩቼቭ ነበር። ሁሉም ስታሊን አደገኝነቱ በዙሪያው ላሉ ፖለቲከኞች ብቻ ሳይሆን ለሩሲያ እንዲሁም ከዛ ባለፈ ለዓለምም ጭምር መሆኑን ተረድተዋል። ቀደም ብሎ በግላቸው ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር የኑክሌር ግጭት ለመጀመር መፈለጉን ግልጽ አድርጎላቸዋል። ሩሲያ ደሃና ደካማ አገር በመሆኗ ጦርነቱን የማሸነፍ ተስፋ እንደሌላት ያውቃሉ። ደሞም በእርግጥ ማንም አሸናፊ አይኖርም። ይህን ወደ አርማጌዴኦን የሚያመራ የዕብደት እርምጃ እስታሊን እንዲጀምር ማንም አይፈቅድለትም። ስለዚህ ስታሊን መሞት አለበት። ወሳኙ ምላጭ ዛሪ ምሽት መሳብ አለበት።

ሪይቢን በዚሁ ማስታወሻው እንደገለጸው የተከበሩ እንግዶቹ አስክ ንጋቱ አስር ሰዓት ቆይተው ሲወጡ እስታሊን ወደ አልጋው አመራ። ኢቫን ክሩስታሌቭ የሚባል በቅርቡ የተሾመ የክብር ዘብ እንባገነኑን አጅቦ ወደክፍሉ ከወሰደው በኋላ ክፍሉን ከውስጥ በላያቸው ላይ ዘጋው። በኋላ ላይ የክብር ዘቡ ለባልደረቦቹ “ በእንደዚህ ሁኔታ የመጀመሪያዬ ቢሆንም…………… ደህና……… ጓድ እስታሊን ምሽቱን ስለማይፈልጉን ሁላችንም ወደመኝታ እንድንሄድ ነግረውኛል ” አለ።

ለነዚህ የደህንነት ሰዎች ዜናው አስገራሚ ነበር። ይህ በጠላቶቹ ጥላ ፍርሃት አድሮበት በማንኛውም ሰዓት እርምጃ የሚወስድ ሰው ሁሌም በ ሃያ አራት ሰዓት የድህንነት ጥላ ውስጥ ነበር የሚኖረው።ጠባቂዎቹ እሱን እንዲጠብቁ ብቻ አይደለም ትዕዛዝ የተሰጣቸው፤ እርስ በእርሳቸውም እንዲሳለሉ ጭምር!!

በጠዋቱ አራት ሰዓት ስለቀኑ ዕቅዳቸው ለመወያየት በወጥ ቤቱ ተሰባሰቡ። በሚያስደንቅ ሁኔታ ግን ይህ ክሩስታሌቭ የተባለ አዲስ ሰው ወደ ቤቱ ሂዷል። የወጥ ቤቱ ቼፍ ጌታው እንደመጣ ቁርሱን ለማሰናዳት በተጠንቀቅ ላይ ነው። ነገር ግን እስከ ጠዋቱ አምስት ሰዓት የስታሊን መምጣት አልታየም። ወዲያው እኩለ ቀን አለፈ…….ሰባት……..ስምት…….ዘጠኝ ሰዓት ። የክብር ጠባቂዎቹ አሁን መጨነቅ ጀመሩ። ነገር ግን ማንም እስታሊንን ከእንቅልፉ በመቀስቀስ ሊረብሸው አልፈለገም። በማያስፈልግ ሁኔታ ከእንቅልፉ መቀስቀስ ቅጣቱ የከፋ ሊሆን ይችላል።

ከምሽቱ አስራ ሁለት ተኩል ላይ ከደህንነት አባላት አንዱ የስታሊን ማረፊያ ክፍል መብራት ማየቱን ተናገረ።አዛዡ ፓቬል ሎጋቼቭ “ ተመስገን አምላኬ!...........ሁሉም ነገር ደህና ነው ” አለ። ለብዙ ሰዓታት መብራቱ መብራቱን ቀጥሏል። እስታሊን ግን ከክፍል አልወጣም። በስጋት የሚናጡት ዘቦች አንዳች እርምጃ ሊወስዱ አልቻሉም። ወዲያው ከምሽቱ አራት ሰዓት ሲሆን መልዕክተኛ ከማዕከላዊ ኮሚቴ መልእክት ይዞ መጣ። ማንኛቸውም መልዕክቱን ይዞ ለመግባት የደፈረ የለም። መልእክተኛው መልእክቱን አሁኑኑ ባይሰጡት ሊደርስባቸው የሚችለውን ቅጣት እንዳይረሱት አስታወሳቸው። ፓቬል ሎጋቼቭ ንግግሩን አቋርጦ ይዞ ገባ።

ከአርባ አራት ዓመታት በኋላ ለስፑትኔክ የሰኔ ወር 1997 ዕትም እንዲህ ሲል ገልጾታል።

“………….እንዲህ አልኳቸው ፤ ‘ ደህና……መልካም ተመኙልኝ…..ልጆች! ’ ብዬ ወደስታሊን ክፍል አመራሁ። ሁሌም ወደሱ ክፍል ስንገባ ድምጽ እያሰማን ነው የምንገባው። በጸጥታ ድምጽ ሳታሰማ ስትገባ እይወድም። በራስህ ተማምነህ እና እርግጠኛ ሆነህ ብዙም አትኩረት ሳትስብ መራመድ አለብህ። ያለዚያ ጥሩውን ወታደር ሽዌክን ማስመሰል እንድታቆም ይነግርሃል።………………… በሩን እስከኮሪደሩ በስፋት ከፈትኩ እና ወደ ትንሿ ክፍል ስመለከት እስታሊን ወለሉ ላይ ተዘርሯል። ቀኝ እጁ ታጥፏል። እንዳየሁት በቅዝቃዜ ደረቅሁ። ልረዳው አሰብኩ። እጆቼ እና እግሮቼ ግን ሊታዘዙኝ አልቻሉም። “ ጓድ እስታሊን …..ምንድ ነው የተፈጠረው? ” ስል ጠየቅሁ። ወዲያው ሰውነቱ በሽንቱ መርጠቡን አየሁ። “ ዶክተር ልጥራ? ” አልኩት። በማጉረምረም “ ዶክ…..ዶክ ” አለ። አዕምሮው ማሰብ አቁሞ ፤የሚናገረውን ጥፍቶበት ነበር።

ሎጋቼቭ መሬት ላይ የወደቀ የፕራቭዳ ጋዜጣ ዕትም እና አስራ ሁለት ሰዓት ላይ መቁጠሩን ያቆመ የኪስ ሰዓት ወለሉ ላይ መውደቁን ልብ ብሏል። ጠረጴዛው ላይ ያልተከፈተ የማዓድን ውሃ በጠርሙስ ይታያል። እስታሊን ሩሁን ስቶ ከመውደቁ በፊት ከአልጋው በመነሳት መብራቱን አብርቶ ውሃውን ለማግኘት መራመዱን ገምቷል።

ሩሲያዊው የታሪክ ጸሓፊ ኤድቫርድ ራድዚንስኪ “ ስታሊን ” በሚለው መጸሃፉ የአይን እማኞችን ቆጥሮ በወቅቱ ስለተፈጠረው ድንጋጤ የተሻለ አብራርቶታል…….

…………በፍርሃት የተወዥናበረው ሎጋቼቭ እራሱን እንደምንም ለማረጋጋት እየሞከረ በግዜው ለሁለት ቀን እረፍት ላይ ለነበረው ለበላይ አለቃው የዳቻ አዛዥ ሻሮስቴን ስልክ ደወለ። አስደንጋጩ ነገር የተነገረው ሻሮስቴን በፍጥነት ወደ ዳቻ በመመለስ ወለሉ ላይ ተጋድሞ የሚያንኮራፋውን አንባገነን በአትኩረት ሲመለከተው ቆየና ምቾት እንዲሰማው በማለት ወታደሮቹ አንስተው ሶፋው ላይ እንዲያስተኙት አዘዛቸው። ቀጥሎም ወደ ኬጂቢ ጽህፈት ቤት ደውለ። ስልኩን ያነሳው የኬጂቢ የበላይ ሃላፊ በድንጋጤ ማንኛውንም ሃላፊነት እንደማይወስድ በመቃወም ተናገረ። እንዲያውም ሻሮስቴን እራሱ ባለፈው ማታ አብረውት ላመሹት እንግዶቹ ማሊንኮቭ እና በሪያ እንዲደውልላቸው ትዕዛዝ አስተላለፈለት። “ እነሱ ምን እንደሚሰሩ ያውቃሉ። ” አለው።

ሻሮስቴን ለበሪያ ደውሎ የደረሰውን ድንገተኛ ሁኔታ ሲገልጽለት እንዲህ አለው። “ ለማንም እንዳትናገር! ጓድ ስታሊን ታመዋል። ”

ሰዓታት ነጎዱ። እየሞተ ያለውን መሪ መጥቶ የሚያየው ባለስልጣን ጠፋ። በላዩ የለቀቀው ሽንቱ ከሶፋው እየተንጠባጠበ የወለሉን ምንጣፍ አራሰው። ይህ ሁሉ ሲሆን የደነገጡ የክብር ጠባቂዎቹ ዙሪያውን ከበው ይመለከቱታል።

ኔኪታ ኩሩቾቭ በጻፈው ማስተዋሻው ደግሞ ከዚህ የተለየ ይነግረናል………..

………… ማሊንኮቭ በድንገት ደወለልኝ። “ ተመልከት! የደህንነት ሰዎች ከስታሊን ቤተ መንግስት ተጨንቀው ይደውላሉ። እስታሊን አንድ ነገር ሳይሆን አይቀርም!፧ ወደዛ ሂድ። እኔም መጣሁ። ለቡልጋኒን እና ለበሪያ ስለደወልኩላቸው እነሱም በአጭር ግዜ ይደርሳሉ። ” አለኝ።

መኪናዬ እንዲዘጋጅልኝ አዘዝኩና ወዲያውኑ ወደ ቤተ መንግስቱ አመራሁ። እግሪ ገና መሪት ከመርገጡ “ ምንድን ነው የተፈጠረው!? ” ስል ዘቦቹን ጠየቅሁ። “ በዚህ ሰዓት ( ከምሽቱ አምስት ሰዓት ) እስታሊን ስልክ ደውሎልን ሻይ ያዝ ነበር። ዛሪ ግን የለም። ” ሲሉ አብራሩልኝ። ”

ክሩቼቭ እንደገለጸው ከባልደረባው ጋር በቀጥታ ወደ ዳቻ ( የስታሊን መኖሪያ ) ሄደ።

“ የዳቻው ዘቦች ጥሩ ያልሆነ ነገር እንደተፈጠረ እና እስታሊንም መኝታው ላይ እንዳለ ነገሩን። እናም በዛ ሁኔታ መመልከቱ ስህተት መስሎ ስለተሰማን ሁላችንም ወደቤታችን ተመለስን። ”

ለአስራ ሶስት ሰዓታት የታላቋ ሶቬት ህብረት የበላይ መሪ ጆሴፍ ስታሊን የህክምና እርዳታ ሳያገኝ እዳሪው ላይ እንደተጋደመ ቀረ። በመጨረሻም ተስፋ የቆረጡ ጠባቂዎቹ ስለደወሉለት ክሩቼቭ አስር ሃኪሞች ወደ ዳቺያ ሄደው እንዲያክሙት ትዕዛዝ ሰጠ። ነገር ግን ራይቢን አስጠርቶ ሲያሳያቸው ሁሉም ወሳኙን ህክምና ለማድረግ ፈሩ። በሚያንኮራፋው አንባገነን ዙሪያ የደም ግፊቱን ለመለካት ወይ ሌላ ምርመራ ለማድረግ ጨንቋቸው እርስ በእርስ ይጠባበቁ ጀመር። እንዲያውም የሚንቀጠቀጠው የጥርስ ሃኪም የበሽተኛውን የፎቶ ፍሪም ሳያስበው መሪት ላይ ጣለው።

አንዱ ሃኪም “ ቪኖግራዶቭ እዚህ መገኘት የለበትም እንዴ!? ” ሲል ጠየቀ። ቪኖግራዶቭ የስታሊን የግል ሓኪም ነበር።ምክትል አዛዡ ሎጋቼቭ ጠጋ ብሎ በሹክሹክታ ፤

“ ያማ አስቸጋሪ ነው። ባለፈው ሳምንት ተይዟል። ” አለው። ይህ ግዜ ብዙዎቹ የህክምና ባለሞያዎች በመንግስት ላይ ታሴራላችሁ በሚል ክስ ወደ ዘብጤያ የሚወርዱበት ወቅት ነበር። እሱም ያ ዕጣ ደርሶታል;

ስታሊንን ሊያክሙት የመጡት ሓኪሞች ሳንባ የሚያሰራ የብረት ማሽን አብሯቸው ነበር። ነገር ግን ፍጹም አልተጠቀሙበትም። የስታሊን ልጅ ስቬትላና እንደገለጸችው “ ያ ትልቅ ነገር ሃኪሞቹ አይናቸውን ከፍተው አፍጥጠው እያዩት ምንም ሳይሰራ አጠገባቸው እንደተቀመጠ ቀረ። ”

በ1972 ዓ/ም የአካዳሚ አባል የነበረው ፕሮፊሰር ማያሲንኮቭ ያንን ግዜ ወደ ኋላ ተመልሶ ሲያስታውስ እንዲህ ይላል።

“………..ማሌንኮቭ እየተፋጠነ ወደ ውስጥ ገባ። ፊቱን አልቦታል። የበሽተኛውን ህይወት ለማስረዘም ማንኛውንም ነገር እንድናደርግ ነገረን። በዛን ሰዓት ሁላችንም የህዝቡን ጭንቅላት ለማዘጋዠት እና አዲስ መንግስት ለመመሥረት ግዜ እንደሚያስፈልግ ገብቶን ነበር። ስታሊን ያንኮራፋል። ባልጋው ላይ እንደተጋደመ ውሉ የጠፋ ሃሳብ ፊቱ ላይ እየበነነ ሲሄድ ይታያል። የማዕከላዊ ኮሚቴ የፕሪዚዲየሙ አባል የሆነው ቮሮሺሎቭ “ ጓድ ስታሊን ሁላችንም ጓደኞችዎ እና ወዳጆችዎ አጠገብዎ ነን። የተከበሩ ጓደኛዬ እንዴት ይሰማዎታል? ”አለው። ነገር ግን የስታሊን አይኖች ስሜታቸውን መግለጽ እያቆሙ ነበር። ቀኑን ሙሉ መርፊ ስንወጋው እና ጋዜጣዊ መግለጫ ስንጸፍ አሳለፍን። የፖሊት ቢሮ አባላት ወደ ሚሞተው ሰው ክፍል ገቡ። የበታች ባለስልጣናት በበሩ አጮልገው ይመለከታሉ። በደንብ አስታውሳለሁ፤ ከነሱ አንዱ ክሩቼቭ ነበር።………..”

ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ከሃምሳ ላይ ከአዶልፍ ሂትለር ያልተናነሰው የጅምላ ጨፍጫፊ አረመኔ እስከወዲያኛው አሸለበ። በመላው ሩሲያና ከዛም ባሻገር ሚሊዮኖች ሊያነቡለት ተዘጋጁ። የምዕራቢያዊያን የምርምር ተቋማት ስታሊን ለሰው ልጅ ላደረገው መልካም ነገር ታላቅነቱን የሚገልጽ አጫጭር ጹሁፎች ፣ መጸሃፍት እና ንግግሮችን በማሰማት አጮሁለት። በሳይቤሪያ እና በሉቢያንካ መታጎሪያ ቦታዎች በግፍ ለሚሰቃዩ ምስኪን እስረኞች ግን የቅዠት ዘመናቸው የሚያበቃበት ግዜ እንደደረስ ተስፋ አደረጉ።

እንግዺህ ከዚህ ሁሉ በኋላ ማንኛውም አንባቢ የሚያነሳው ጥያቄ ይኖራል። ምንድ ነው በዕርግጥ እስታሊን ላይ የደረሰው? ኦፊሻሊ እንደተነገረው ጭንቅላቱ ውስጥ የደም መፍሰስ ስላጋጠመው ነው የሞተው? ወይስ በሰው ተገደለ?

ያኔ ዕውነቱ ባይታወቅም እስታሊን ተመርዞ ለመሞቱ የሚገልጹ የሩሲያና የምዕራቢያዊያን የታሪክ ተመራማሪዎች እየተበራከቱ ነው።ሁሉም እንደሚሉት ጓደኞቹን በግዜ ወደመኝታቸው እንዲሄዱ የነገራቸው አዲሱ የክብር ዘብ ክሩስታሌቭ የአንባገነኑን ነፍስ ለመሸኘት ተንቀሳቅሷል። ከአለቃው የኬጂቢ ሃላፊ ላቭሪንትይ በሪያ በደረሰው ትዕዛዝ መሠረት የተኛውን አንባገነን በሰው ልጅ ላይ የጭንቅላት ደም መፍሰስ የሚያስከትለውን የአይጥ መርዝ ሳይወገው እንዳልቀረ ተገመቷል።

Stalin’s Last crime በሚለው መጻሃፋቸው ፕሮፊሰር ብረንት ሲገልጹ፤ ማሌንኮቭ፣ በሪያ፣ ክሩቼቭ እና ቡልጋኒን አንባገነኑን ለማስወገድ የተደረገውን ሴራ ለማሳካት ባለ ኃይላቸው ተንቀሳቅሰዋል። ስታሊን እራሱ ዕቅዱን በገለጸው መሰረት ሁለተኛውን ሽብር በመጀመር በመቶ የሚቆጠሩ የፓርቲ ባልደረቦቹን እና ሌሎች በአስር ሚሊዮን የሚቆጠሩ ሩሲያውያንን ለመጨፍጨፍ ተዘጋጅቷል። ከዚህ ሁሉ የከፋው አደገኛ ነገር ግን መላውን ዓለም ለማጥፋት ማቀዱ ነበር። አራቱ ሴረኞች ከራሳቸው ህይወት የበለጠ ያስፈራቸው የኑክሌር እልቄት እርምጃውን እንዲወስዱ አድርጓቸዋል ይላሉ ብራንት።

የ Stalin መጸሃፍ ደራሲ ኤድቫርድ ራድዚንስኪ ከ ፓቬል ሌጋቼቭ ጋር ያደረጉትን ንግግር እንዲህ ሲል ዘግቦታል።….

“…………….እስታሊን ከመሞቱ ከሳምንት በፊት ‘ አሜሪካ ትወረናለች ብልህ ታስባለህ? ’ ሲል ጠየቀኝ። እንደማይደፍሩ መለስኩለት። ያ - አበሳጨው። በኋላ ላይ ወደ እኔ መጥቶ እንዲህ አለኝ። ‘ አዎ!....ይወሩናል!! ’

እንደዛ ሲለኝ በግልጽ ከፊቱ ላይ እንደዛ እንዲሆን መፈለጉን ማንበብ ችዬ ነበር። ”

የሆኖ - ሆኖ ይህ የWorld’s Great Mysteries ደራሲ ስለ ስታሊን አሟሟት የሚተርከውን ምዕራፍ የሚዘጋው አንባገነኑ በተፈጥሮ ሞት ይሙት ወይ በባልደረቦቹ ሴራ ተጠልፎ በመመረዝ፤ ሞቱ ግን በዓለም ታሪክ ታይቶ የማያቅ ሊመጣ የነበረውን የሰው ልጅ ዕልቄት ማስቀረት ችሏል።

Wednesday, November 10, 2010

ሞት ይርሳኝ!

                   መጻፍ ናፈቀኝ! ይቼ…….ከቀደድኩባት ሁለት ወራት ያለፉባት መቅደጃዬ ትዝ አለችኝ።ብቸኝነቴን ከምደበቅባቸው እና የሚሰማኝን ቀድጄ ልክ ለሚወዱት ጟደኛ ኃሳብን ተንፍሶ እፎይ የማለት ስሜት የምትጭርብኝን ብሎጌን ከረሳኋት ቆየሁ። ሞት ይርሳኝ!...........ብሎጌ ዓለምም ርስቷት፡ በእኔ ባለቤቷም ጭምር ተረስታ ዘመናት ያለፉ መሰለኝ!

                  ግና እንዴያ አልነበረም። ዛሬ የአንባቢያኗን ቁጥር ለማወቅ ዌብ ስታትዋን ከፍቼ ስመለከት ውጤቱ አግራሞት ጫረብኝ። ባለፉት ሁለት ወራት አዲስ ጹሁፍ አለማቅረቤ አንባቢዎቼን እንዲሁም እራስዋን ብሎጌን የከዳኋት አይነት ስሜት ተሰማኝ።

                 በዚህ ከርስ ለመሙላት ላብ እንጩፍ በሚደረግበት ቁሳዊ ዓለም ከጠዋቱ አስር ሰዓት ከእንቅልፊ ተነስቼ ወደስራዬ እሄዳለሁ፤ ከዛ መልስ ወደትምህርት ቤት። ከምሸቱ አራት ሰዓት ወደ ቤቴ ስመለስ አካሌ ዝሎ፣ አእምሮዬ ላሽቆ መኝታዬን በስስት እየናፈቅሁ የምተኛውን እንቅልፍ አሰላስላለሁ። እዚህ ህይወት በማሽን መልክ ሊመሰል ይችላል። የኃይል አቅርቦት ካልተቋረጠበት በስተቀር ሳያሰልስ እንደሚዘውር ማሽን! ሁሌም ከሰኞ እስከ አርብ እንዴሁ ነው። ………….

                 የውድ ባለቤቴን ከንፈር ስሜ፣ ምርቃቷን ተቀብዬ ስወጣ ክዋክብት የፈንጠቁበት ጨለማ “ እንደምን አደርክ! ” ብሎ ይቀበለኛል። ማታም ከጨለማው እና ከክዋክብቱ ጋር “ ደህና እደር!......ደህና እደሩ! ” ተባብለን ባዛው መልኩ እንለያያለን። ቅዳሜ እና እሁድ እረፍት ብሆንም አብዛኛውን ሰዓት በመተኛት እና በማጥናት እንዲሁም የተረፈችውን ግዜ ከባለቤቴ ጋር “ ድራፍት ቢራ ” እየጠጣን ልንጨዋወትባት ተያይዘን እንወጣለን።

                ብዙውን ግዜ እዚህ ቤዩርጋርድ እስትሪት የሚገኘው “ ክላይድ ” የሚባለው ሬስቶራንት እንሄዳለን። ረጅም ጸጉሩን ወደኋላ ማሲያዝ የሚወደው የሬስቶራንቱ ባሬስታ እስካር፤ ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ ፤አበሾች “ ሳሙኤል አዳሙ ” የሚሉትን ዝነኛ የላጋር ቦስተን ድራፍት ቢራ በብርጭቆ አምጥቶ አጠገባችን በማስቀመጥ “ here you go! ” ይለናል። ሁሌም ድርጊቱ በቴሌቭዥን የሚተላለፈውን የበድቫይዘር ቢራ ማስታወቂያ ያስታውሰኝል።

             በአረፋ የተሞላውን ወፍራም የቀዘቀዘ ድራፍት ብድግ አድርጌ ጉንጭት ሳደርገው ነፍሴ በፍስሃ ትሞላለች። ታዲያ ግንባሪ ወዲያው ወዝቶ የውስጥ ደስታዬን ያሳብቅብኛል።

“ በቃ!.........ድራፍትህን አገኝህ……….አቤት ደስታህ! ማን ይቻልህ!? ” ትለኛለች ፊቴን ያነበበችው ባለቤቴ።

ጠጬ አይደለሁም። ከሁለት ብርጭቆ በላይ የጠጣሁባቸው ግዜያቶችን ብዙም አላስታውሳቸውም። ሆኖም ስጠጣ እያንዳንዱን ጉንጭ እያጣጣምኩ እና እየተደሰትኩበት ቁልቁል ወደ ውስጤ እልከዋለሁ። እዚህ አገር በፍቅር ከወደድኳቸው ነገሮች እንደ ስታር ባክስ ቡና እና እንደዚሁ የድራፍት ቢራ መሰል ምን አለ!?

………….. በእርግጥ ተወዳዳሪ የሌለው ደስታዬ ያው ማንበብ ነው። የማነባቸው መጸሃፍት ሁሌም ሃሳብ ይጭሩብኛል። ሃሳብ ደግሞ “ ጻፈኝ እና ሌላውም ያንብበኝ! ” የሚል ሙግት ውስጤ ይፈጥራል። ማንም ባያነበው እንኳ እዝችው መከረኛ ብሎግ ላይ ለጥፊያት በቃ!......ይቅለለኝ። አሁን የምጽፍበት ኮምፒዩተር የተቀመጠበት ዴስክ ላይ አንድ ስድስት የሚሆኑ መጸሃፍት ተሰትረዋል።

             Unstrung Heroes, The ultimate Encyclopedia of Mythology, የ ጥንታዊቷ ቻይና ዝነኛ ፈላስፋ የሆነው የSun Tzu ‘ ዝነኛ መጸኃፍ ’ The Art Of War እንዲሁም አግራሞትን የፈጠረብኝ World’s Great Mysteries ኮምፒዩተር ላይ በተቀመጥኩ ቁጥር ያፈጡብኛል። ዛሪ ከራሴም ከብሎጌም እርቅ ማድረግ አለብኝ። ምንም ኑሮ በራሱ ሳንክሳር ቢጨናነቅም በሁለት ሳምንት አንዴ ብሎጌን የማወያያት አንዳች ኃሳብ…..ጹሁፍ ይዤ ማምጣቴ አይቀርም! ከብሎጌ ጋር እርቅ የማደርገው ግን ከእነዚህ መጸሃፍቶች በአንዱ ተንተርሼ በማቀርበው ጹሁፍ ይሆናል። የቅዳሜ ሰው ይበለን!

Monday, October 25, 2010

I Like You When You Are Quiet

Pablo Neruda

I like you when you are quiet because it is as though you are absent,
and you hear me from far away, and my voice does not touch you.
It looks as though your eyes had flown away
and it looks as if a kiss had sealed your mouth.

Like all things are full of my soul
You emerge from the things, full of my soul.
Dream butterfly, you look like my soul,
and you look like a melancholy word.

I like you when you are quiet and it is as though you are distant.
It is as though you are complaining, butterfly in lullaby.
And you hear me from far away, and my voice does not reach you:
let me fall quiet with your own silence.

Let me also speak to you with your silence
Clear like a lamp, simple like a ring.
You are like the night, quiet and constellated.
Your silence is of a star, so far away and solitary.

I like you when you are quiet because it is as though you are absent.
Distant and painful as if you had died.
A word then, a smile is enough.
And I am happy, happy that it is not true.